የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለ 2014 አም የኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ለማስተናገድ የሚፈልጉ ካሉ ጥያቄውን በደብዳቤ አሳወቀ።

#የኢትዮጵያ_እግር_ኳስ_ፌዴሬሽን ለ 2014 አም የኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ለማስተናገድ የሚፈልጉ ካሉ ጥያቄውን በደብዳቤ አሳወቀ።

✍ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ስር ከሚደረጉ ውድድሮች ውስጥ አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ውድድር በወንድና በሴት ለሚደረገው የ 2014 አም ውድድር ለማዘጋጀት ፍላጎት ላላቸው በደብዳቤ ጥያቄ ያሳወቁ ሲሆን በ 2013 አም በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማ አስተናጋጅነት መከናወኑ ይታወቃል። ፌዴሬሽኑ የዘንድሮውን ለማስተናገድ ለሚፈልጉ ክልሎች ጥያቄውን የላከ ሲሆን ውድድሩን ለማከናወን ሊሟላ የሚገባ መስፈርቶችን በዝርዝር ገልፅዋል።

 ለማስተናገድ ሊሟሉ የሚገባቸው

1. በቂ የመወዳደሪያ ሜዳና የልምምድ ሜዳ ያለው
2. በቂ የመኝታ አገልግሎት እና የምግብ አቅርቦት ያለው
3. የተሟላ የፀጥታ ሁኔታን ማመቻቸት የሚችል
4. በቂ የሆነ የህክምና አገልግሎት መስጠት የሚችል
5. በቂና የማይቋረጥ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ያለው
6. በአጠቃላይ በሁሉም በቂ መስተንግዶ ለማድረግ ፍቃደኛ የሆነ

 የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሊሟሉ የሚገባቸው ዝርዝር መስፈርቶችን በማቅረብ አሳውቋል።

✅ በ 2013 አም የውድድር አመት የሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማ ውድድሩን በሚገባ እንግዶቿን አስተናግዳና ከበቂ በላይ ሜዳዎችን በማቅረብ ውድድሩ በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቋ አይዘነጋም። የወንድሮ አስተናጋጅ ሁኖ የሚመረጥ ከተማ ከሀዋሳ ከተማ የተሻለ ልምድ በመውሰድ የተሳካ ውድድር እንዲያስተናግዱ #ዳጉ_Sport ምኞቷል ለመግለፅ ትወዳለች።

✍ ለበለጠ መረጃ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን T.me/Dagu_Sport ይቀላቀሉ።

©️ ዳጉ Sport by Nuru Kadaba

AFCON2021 የፍፃሜ ጨዋታዎች ዳሰሳ

AFCON2021 የፍፃሜ ጨዋታዎች ዳሰሳ

በካሜሮን አስተናጋጅነት ከጥር 1/2014 ጀምሮ ሲደረግ የነበረው የአፍሪካ ዋንጫ በሴኔጋል አሸናፊነት ፍፃሜውን አግኝቷል፡፡ ለደረጃ የተደረገውን ጨዋታ ደገሞ ካሜሮን አሸንፋለች፡፡ እንዚህን ጨዋታዎች እና አጠቃላይ ውድድሩን የምንዳስስበት የመጨረሻ ፅሁፋችን ነው

የፍፃሜ እለት ይደረጋል ተብሎ ቀጠሮ ተይዞለት የነበረው የካሜሮንና ቡርኪናፋሶ የደረጃ ጨዋታ በአንድ ቀን ቀረብ ብሎ ከግማሽ ፍፃሜው ጨዋታ ብዙም እረፍትና ማገገም ሳይኖረው ነበር የተደረገው፡፡ ለዚህም ይመስል ነበር ካሜሮኖች ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪያቸውን ቪንሰንት አቡበከርን መጠባበቂያ ወንበር ላይ አስቀምጠው ጨዋታውን የጀመሩት፡፡ሁለቱ ቡድኖች በውድድሩ ጅማሮ አንድ ምድብ ላይ ሆነው የመክፈቻ ጨዋታ ያደረጉ እንደሆነ የሚታሰብ ሲሆን በፍፃሜውም ጨዋታ ይገናኙና የመዝጊያ ጨዋታ ይሀናል የሚለውን ግምት ሳያሳኩ ቀርተው ነው ከመዝጊያ በፊት በሚደረግ የደረጃ ጨዋታ የተገናኙት፡፡ በመጀመርያ የምድብ ጨዋታቸው አዘጋጇን ካሜሮንን በሜዳዋና በህዝቧ ፊት በአንድ ጎል ስትመራ ቆይታ ቆይታ ሁለት ጎል ተቆጥሮባት ሁለት ለአንድ የተሸነፈችው ቡርኪና ፋሶ ምናልባት ይህ የመበቀያ እድሏ እንደሚሆን ተገምቶ ነበር፡፡ እስከ 72ኛ ደቂቃው ድረስ የነበረው የጨዋታ ሂደትም ይህንን የሚመሰከር ሀቅ መስሎ ነበር፡፡ ቡርኪና ፋሶዎች በምድብ ጨወታቸው ካሜሮን ላይ ባስቆጠሩት አይነት የጨዋታ እንቅስቃሴ በተከላካያቸው ስቲቭ ያጎ አማካኝነት በ24ኛው ደቂቃ የመጀመርያ ጎል አስቆጠሩ፡፡ ከግብፁ የግማሽ ፍፃሜ ሽንፈት ስነልቦና ምንም ያላገገሙ የሚመስሉት ካሜሮኖች ምንም አይነት ምላሽ የመስጠት ፍላጎት አላሳዩም፡፡ ይባስ ብሎ በ43ኛው ደቂቃ ላይ በቀኝ የጎል መስመር በኩል ሌላኛው ወጣቱ የማችስተር ሲቲው በውሰት ለፈረንሳዩ ኢ.ኤስ ትሮየስ የሚጫወተው ተከላካካይ ኢሳ ካቦሬ ኳሷን ከመውጣት ታድጎ ያሻገራትን ግብ ጠባቂው አንድሬ ኦናና በራሱ ግብ ላይ አስቆጠራት፡፡ የመጀመርያው አጋማሽ በቡርኪናፋሶ 2 ለ 0 መሪነት ተጠናቆ ወደ መልበሻ ክፍለ ገቡ፡፡ አብዛኛው ተመልካች ውጤቱ በቡረኪናፋሶ አሻናፊነት እንደሚጠናቀቅ እምነት አሳደረ፡፡ የዚህ ማረጋገጫ ደግሞ ካሜሮኖች የቁርጥ ቀን ልጃቸው ቪንሰንት አቡበከርን ከእረፍት መልስ ቀይረው አስገብተው የነበር ቢሆንም በ49ኛው ደቂቃ አጥቂው ጅበሪል ኦታራ ከትራኦሬ የተሸገረለትን ኳስ አስቆጥሮ ውጤቱን ወደ 3ለ0 ማድረጉ ለካሜሮናውያን የበለጠ ተስፋ አስቆራጭ ሆነ፡፡ ይህ ግን እስከ 72ኛ ደቂቃ ነበር የቆየው፡፡ ካሜሮናውያን ተስፋቸው ማቆጥቆጥ የጀመረበትን ጎሎ በአጥቂያቸው ስቴፈን ባሆኮን አማካኝነት አስቆጠሩ፡፡ ጨዋታው 3ለ1 ሆነ፡፡ ሰዓቱ ግን በቂ አልነበረም፡፡ ልክ 85ኛ ደቂቃ ላይ ልማደኛወ አጥቂ ቪንሰንት አቡበከር ጎል አስቆጥሮ ውጤቱ ምናለባት ሊገለበጥ እንደሚችል የመጨረሻ ተስፋ ሰጠ፡፡ ይህም አልቀረም 87ኛው ደቂቃ ላይ አሁንም ቪንሰንት አቡበከር አቻ ምታደረገውን ጎል አስቆጥሮ የቸዋታው ታሪክ ተቀየረ፡፡ ሙሉ 90 ደቂቃው 3ለ3 በሆነ ውጤት ተጠናቆ ወደ መለያ ምቶች አመራ፡፡ በመለያ ምቱም ካሜሮን 5ለ3 በሆነ ውጤት የ3ኛት ደረጃ ጨዋታውን በአሸናፊነት አጠናቀቀች፡፡ ለካሜሮናውያን ጣፋጭ ድል ለተመልካች በስሜት ውጣውረድ የተሞላ አና አዝናኝ ጨዋታ ነበር፡፡ ቪንስንት አቡበከር በውድድሩ ያስቆጠራቸውን ጎሎች 8 አድርሶ ከፈረንጆቹ 1974 የግብፁ የአፍሪካ ዋንጫ ወዲህ በመድረኩ በዙ ጎሎች ያሰቆጠረ ተጫዋች ሆኗል፡፡በቀድሞ ስሟ ዛየር በአሁኑ ዲ.ሪ. ኮንጎ ባሸነፈችበት በዚህ ውድድር ዳዬ ሙላምባ የተባለ ተጫዋቿ 9 ጎሎች ነበር ያስቆጠረው፡፡

በተጠባቂው የግብፅና ሴኔጋል የፍፃሜ ጨዋታ ብዙ  ክስተቶች የተስተዋሉበት ሲሆን በጨዋታው በ7ኛ ደቂቃ ላይ የተሰጠውን ፍፁም ቅጣት ምት የመድረኩ ክስተት ነበረው የግብፁ ግብ ጠባቂ ጋባስኪ የሳዲዮ ማኔን ምት አድኗል፡፡ የሊቨርፑል የቡድን አጋሩ ሞ ሳላህ ለጋባስኪ የሳዲዮ ማኒን ቴክኒክ በሚናገርበት ወቅት ሳዲዮ ማኒ ወደ ሁለት ቀርቦ ውይይታቸውን የተሳተፈበር ሂደት አነጋጋሪ ነበር፡፡ የሞሳላህ ምክር ሰርቶ ግብፅ ጎል ሳይቆጠርባ 120 ደቂቃዎ እንድትቆይ አድጎ ነበር፡፡ ግብፆች በግብ ጠባቂያቸው ፍፁም ቅጣት የማዳን አቅም በመተማመን ሴኒጋሎችም በቼልሲው በወቅቱ የፊፋ ኮከብ ግብ ጠባቂ በመተማመን ወደ መለያ ምት ባመሩት ጨዋታ ያልተጠበው ሆኖ ግብፆች በአብዱልሞኔም እና በላሼን አማካኝነት ሁለት ስተው ሴኔጋሎች ደገሞ በሳር አማካኝነት አንድ ብቻ ስተው የሁለቱ ሀያላን ፍልሚያ በሴኔጋል በመለያ ምት 4ለ2 በሆነ ውጤት ተጠናቋል፡፡  ይህንን ተከትሎ ሴኔጋል በታሪኳ ለመጀመርያ ጊዜ የአፍሪካን ዋንጫ በልታ ዋንጫ ከበሉ 15 ሀገራ መዝገብ ላይ ስሟን አስፍራለች፡፡ ለተከታታይ 8 አመታት በአሰልጣኝነት የአፍሪካ ዋንጫውን ትኩርት አድርጎ የሰራው የቀድሞ ተጫዋቿ የአሁኑ አሰልጣኝ አሊዩ ሲሴ ትኩረት ያገኘ ግለሰብ ሆኖ አምሽቷል፡፡ በውድድሩ ፍፃሜ ግብፆች እንባቸውን መቆጣጠር እስኪያቅታቸው ያነቡ ሲሁን በተቃራኒው ሴኔጋሎች የሚያደርጉትን እስካማያውቁ ድረስ በደስታ ሲፈነጥዙ አምሽተዋል፡፡በዚህ ጨዋታ የግብፁ ግብ ጠባቂ ጋባስኪ የማኔን ፍጹም ቅጣት ምት ጨምሮ በርካታ ጎል ሊሆኑ የሚችሉ ኳሶችን በማዳኑ የጨዋታው ኮከብ ተብሏል፡፡

በውድድሩ

  1. ቪነስንት አቡበከር ኮከብ ጎል አግቢ
  2. ሳዲዮ ማኔ ኮከብ ተጫዋች
  3. ሜንዲ ኮከብ ግብ ጠባቂ

በመባል ሽልማታቸውን ወስደዋል፡፡

©️ ዳጉ Sport by ወሰን ጴጥሮስ

✍ በአሰልጣኝ አንተነህ አበራ የሚመራው ጅማ አባ ቡና አራት አዳዲስ ተጫዋቾችን አስፈረመ።

💶ጂማ አባ ቡና አዳዲስ ተጫዋቾች አስፈረመ💷

✍ በአሰልጣኝ አንተነህ አበራ የሚመራው ጅማ አባ ቡና አራት አዳዲስ ተጫዋቾችን አስፈረመ።

✅ በምድብ ሶስት ተደልድሎ የአንደኛ ዙሩን ጫዋታ በጅማ ከተማ ያከናወነው ጅማ አባ ቡና በዙሩ ባረገው ዘጠኝ ጫዋታ አንድ ጫዋታ በማሸነፍ በስድስቱ ነጥብ ተጋርቶ በሁለቱ ሽንፈት አስተናግደው በዘጠኝ ነጥቦች ምድባቸውን በሰባተኝነት ዙሩን ማጠናቀቃቸው አይዘነጋም።

✅ ክለቡ ለማጠናከር ባሁኑ ሰአት አራት ተጫዋቾችን ማስፈረም ሲችል ሁለት ተከላካዮች አንድ የመሀል ስፍራ ተጫዋችና አንድ የፊት መስመር አጥቂዎችን በማስፈረም ቡድናቸውን ማጠናከር ችለዋል።

ወደ ጅማ አባ ቡና የተቀላቀሉት ስም

  1. ንጋቱ ጎዶቤ ከ ቤንች ማጂ ቡና
  2. አብዱልከሪም ከ ኮልፌ ቀራንዮ
  3. ደረሰ ሞላ ከ ወልድያ ከተማ
  4. በረከት ከ ነገሌ አርሲ ሲሆኑ እነዚህ አራት ተጫዋቾች ለጅማ አባ ቡና እግር ኳስ ክለብ መፈረማቸው ዳጉ Sport ያገኘችው መረጃ ያመላክታል።

©️ ዳጉ Sport

AFCON 2021 Cameroon የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዎች ዳሰሳ

AFCON 2021 Cameroon የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዎች ዳሰሳ

ሁለት ጨዋታች በቀሩት የካሜሮኑ የአፍካ ዋንጫ በአስገራሚነቱ እንደቀጠለ ሲሆን ረቡዕ እና ሀሙስ የተደረጉ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዎች ውድድሩ ምን ያህል ጠንካራ፣ አዝናኝና እና ትኩረት ሳቢ እንደነበር ምስክር ነው፡፡

ረቡዕ እለት በስቴድ አህማዱ አህዲጆ ሰታድየም በኢትዮጲያዊው ዳኛ በአምላክ ተሰማ የተመራው የቡርኪና ፋሶ እና ሴኔጋል የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ በሴኔጋል 3ለ1 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡ ጨዋታውን በድል ከተወጡት ከሴኔጋል ኳክብት ባልተናነሰ የእለቱ ዳኛ ያሳዩት ብቃት በተለያዩ አለም አቀፍ ሚዲያዎች እና በስፖርት ቤተሰቡ መነጋገሪያ ሆኖ ሰንብቷል፡፡ የጨዋታው ፍክክር የሀይል ሚዛን ያደላበትና ግጭቶች የበዙበት ቢሆንም በተረጋጋ እና በስክነት ውሳኔዎችን ሲወስኑ የነበሩት በአምላክ ተሰማ ሁለት አሳሰሳች የነበሩ የፍፁም ቅጣት ምት ይገባኛሎችን በቫር በመታገዝ ሳይሰጡ ቀርተዋል፡፡ እንደተጠበቀው የግጭትና የጉልበት ትንቅንቁ ያየለበት ጨዋታ የመጀመርያ አጋማሽ ያለምንም ጎል ቢጠናቀቅም በሁለተኛው አጋማሽ ሴኔጋሎች በ70ኛ እና 76ኛ ደቂቃዎች ላይ የፒ.ኤስ.ጂው አብዱ ዲያሎ እና የአሎምፒክ ማረሴው ባምባ ዲዬንግ አከታትለው ባስቆጠሩት ጎል ሁለት ለምንም መምራት ቻሉ፡፡ ቡርኪናፋሶዎች ተስፋ ባለመቁረጥ ወደጨዋታ የመመለስ ጥረታቸው ተሳክቶላቸው በ82ኛ ደቂቃ ላይ በብላቲ ቱሬ አማካኝነት ጎል አግብተው የአቻነት ጎል ፍለጋ መሯሯጥ ጀመሩ፡፡ ነገር ግን ይህ ተስፋቸው የቆየው ለ5 ደቂቃዎች ያህል ብቻ ነበር፡፡ ሴኔጋሎች በ87ኛ ደቂቃ ላይ በሊቨርፑሉ ኮከባቸው በሳይዶ ማኔ አማካኝነት ጎል አስቆጥረው ጨዋታው 3ለ1 በሆነ ውጤት ተጠናቋል፡፡ ሳድዮ ማኒ በውድድሩ ያስቆጠራቸው ጎሎች ብዛ ሶስት ሆነውለታል፡፡ውጤቱን ተከትሎ ቡርኪና ፋሶዎች ቅዳሜ ለደረጃ ሲጫወቱ ሴኔጋች እቅዳቸው ተሳክቶ እሁድ ጥር 29 ለፍፃሜ ለዋንጫ ይጫወታሉ፡፡

የቀጣዩ ቀን ተናፋቂው የአዘጋጇ ካሜሮንና የግብፅ ጨዋታ ነበር፡፡ ከመጀመሩ በፊት  ውጤቱን ለመገመት አስቸጋሪ የነበረው ይህ ጨዋታ እንደግምቱ ሁሉ120 ደቂቃዎችን ያለምንም ጎል ነው የተጠናቀቀወ፡፡ አሸናፊውን ለመለየት ከተሰጡትን አምስት አምስት መለያ ምቶች ውስጥ በኮትዲቯሩ ጨዋታ የኤሪክ ቤይሊን ምት አድኖ ግብፅን ያሳለፋት ከሞሮኮው ጨዋታ ጉዳት ብዙም ሳያገግም የሀገር ፍቅር አስገድዶት ወደ ጨዋታ የገባው ግብ ጠባቂው መሀመድ ቆትብ አቡ ጋባል ጋባስኪ  የካሜሮኖቹን የሞኩንዲን፣ ሊያ ሲሊኪና ጂዬን ምቶች አድኖ ግብፅ 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፋ ለዋንጫው ጨዋታ እንድታልፍ አድርጓታል፡፡ ጨዋታው በብዙ ቁጥር የካሜሮኖች የበላይነት የነበረው ቢሆንም የግብፆች አልሸነፍባይነት ለብዙ ሀገር ተጫዋቾች እንደሞዴል የሚጠቀስ ሆኖ አልፏል፡፡

ለደረጃ በሚደረግ የቅዳሜ ጨዋታ ከኢትዮጲያ ጋር በምድብ ድልድሉ የነበሩት ካሜሩንና ቡርኪና ፋሶ የሚገናኙ ሲሆን በምድብ ጨዋታቸው ካሜሮኖች ከመመራ ተነስተው በቪንሰንት አቡበከር ሁለት ጎሎች 2ለ1 ማሸነፋቸው ይታወቃል፡፡

እሁድ በሚደረግ የፍፃሜ ጨዋታ አለም በጉጉት እንዲጠብቀው ባደረገው ክስተት ሁለቱ የሊቨርፑል ኳክብት ሞ ሳላህ እና ማኔ በተቃራኒ የሚገናኙበት የግብፅ እና የሴኔጋል ጨዋታ ጥሩ ፉክክር እንደሚታይበት የሚገመት ሲሆን የቡድን ጓደኛማቾቹ ለሀገራቸው የሚያደርጉት አስተዋፅኦም የሚለካበት ይሆናል፡፡

ሴኔጋል ለፍፃሜ የደረሰቸው

በምድብ ቢ ጨዋታ ዚምባብዌን 1ለ0 አሸንፋ፣ ከጊኒና ማላዊ አቻ ውጥታ በ5 ነጥብ 1ኛ ሆና ከምድብ አልፋ፣ በ16 ውስጥ ጨዋታ ኬፕ ቨርዴን 2ለ0 አሸንፋ፣ በሩብ ፍፃሜ ጨዋታ ኢኳቶሪያል ጊኒን 3ለ1 አሸንፋ እና በግማሽ ፍፃሜው ጨዋታ ቡርኪና ፋሶን 3ለ1 አሸንፋ ነው፡፡

ግብፅ ልፍፃሜ የደረሰችው

በምድብ ዲ ጨዋታ በናይጄርያን 1ለ0 ተሸንፋ፣ ጊኒቢሳኦንና ሱዳንን በተመሳሳይ 1ለ0 አሸንፋ በ6 ነጥብ 2ኛ ሆና ከምድብ አልፋ፣ በ16 ውስጥ ጨዋታ አይቮሪኮስትን በመለያ ምቶች አሸንፋ፣ በሩብ ፍፃማ ጨዋታ ሞሮኮን 2ለ1 አሸንፋ እና በግማሽ ፍፃሜው ጨዋታ ካሜሩንን በመለያ ምቶች አሸንፋ ነው፡፡

©️ ዳጉ Sport

በሽልማት የተበረከተለቴን መሬት በመሸጥ ለሚወደው እግር ኳስ ያበረከተ አሰልጣኝ።

✅ በሽልማት የተበረከተለቴን መሬት በመሸጥ ለሚወደው እግር ኳስ ያበረከተ አሰልጣኝ።

መኮነን ገላነህ (ዊሀ) ማነው ?

👉 ይህ አሰልጣኝ በተጫዋችነትም በአሰልጣኝነቱም የተሳካለት ነበር።
ይህ ሰው የአርባምንጭ ከተማ ፍሬ የህነው #መኮነን_ገላነህ በቅፅል ሱሙ #ዊሀ ይባላል ።
እግር ኳስን በተጫዋችነት 1989 አም እስከ 2001 አም ተጫውቶ ያለፈ ሲሆን በተጫዋችነት ጊዜው በታላላቅ ክለቦች አገልግሎት ሲሰጥ የተጫወተባቸው ክለቦች ደግሞ ከታች ተዘርዝረዋል።
👇 በክለብ ደረጃ የተጫወተባቸው ቡድኖች
✅ ሀዋሳ ከተማ
✅ አርባምንጭ ጨርቃ ጨርቅ
✅ ወንጂ ስኳር
✅ ሐረር ቢራ
✅ አዳማ ከተማ
✅ ኦሜድላና
✅ ሻሸመኔ ከተማ ለ 13 አመታት መጫወት የቻለ ሲሆን ለብሄራዊ ቡድን ደግሞ በተለያዩ የእድሜ እርከኖች ተጫውቷል።
✅ ከ 17 አመት በታች
✅ ከ 20 አመት በታች
✅ ከ 23 አመት በታች ለኦሎምፒክ እና ለዋናው ብሄራዊ ቡድን አገልግሏል።

✍ በተጫዋችነት ስኬታማ ጊዜን ያሳለፈው ይህ አሰልጣኝ ከተጫዋችነት ወደ አሰልጣኝነት በመግባት ያለው የጠለቀና የረዥም ጊዜ የጫዋታ ልምድ ለማካፈል ቆርጦ በመነሳት በ 2002 አም #Weax 95 እግር ኳስ ፕሮጀክት በአርባምንጭ ከተማ ማቋቋም ችሏል።
ከዛም አልፎ በእግር ኳስ ተጫዋችነቱ የሰበሰባቸውን ገንዘብ ላቋቋመው ፕሮጀክት የተለያዩ የስፖርት ቁሳቁስ ግዢ አውሏል።
ያቋቋመው ፕሮጀክት ከ 15 አመት በታች ሲሆን በወንድ 30 በሴቶች 30 ባጠቃላይ 60 ሰልጣኞች በፕሮጀክቱ አቅፎ ማሰራት ችሏል። በዚህ ጉዞላይ ግን መሀል ላይ የፋይናንስ እጥረት ገጠመው እሰከ አሁን ከራሱ ያለውን ብር ተጠቅሞ ተጉዞ ነበር አሰልጣኞቹ የስፖርት ቁሳቁስ በመጨረሳቸው ይህ አሰልጣኝ ከባድ ውሳኔ ወሰነ ። የጀመረውን ፕሮጀክት እንዳይቆምና እንዳይፈርስ በማሰብ በተጫዋችነት ወቅት ለ አርባምንጭ ጨርቃጨርቅ ቡድን ባረገው ተሳትፎና ባገኘው ዋንጫ ምክንያት በጋሞ ዞን አስተዳደር አማካኝነት በ አርባምንጭ ከተማ በሽልማት መልክ የተበረከተለትን መሬት በመሸጥ ለፕሮጀክቱ በማዋል ያሰበውን ምኞት በማስቀጠል በርካታ ታዳጊዎች ለሀገር አብቅቷል። በዚህ ፕሮጀክት 6 የውጣ ውረድ አመታት በማሳለፍ የልፋቱን ፍሬ ማየት ሲችል እስከ 2008 የ Weax 95 ፕሮጀክት ውጤት የሆኑት ከብዙ በጥቂቱ ለአብነት ያክል ከታች የተዘረዘሩት ተጫዋቾች ማለትም
✅ ይሳቅ ተገኝና
✅ በላይ ገዛኸኝ ለአርባምንጭ ከተማ ሳበቃ
✅ አረጋሽ ካሳና
✅ ቤቴሊሔም ታምሩ ደግሞ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ለብሄራዊ ቡድኑ ተመርጠው ተጫውተዋል።
👉 በ 2008 አም በመላው ኢትዮጵያ ልዩ ልዩ ውድድር ላይ የደቡብ ክልል የሴቶች እግር ኳስ በአሰልጣኝነት በመያዝ 3ኛ ደረጃ በማስያዝ የነሐስ ሜዳልያ ተሸላሚ መሆን ችሏል።

✍ ከክልል ውድድር መልስ በክለብ ደረጃ በሁለተኛ ዙር ለመጀመሪያ ጊዜ ጎፋ ባሬንቼን በአሰልጣኝነት በመረከብ መልካም የሚባል አመት ከጥሩ እንቅስቃሴ ጋር የተሻለ ቡድን መስራት ችሏል።

✍ በ 2009 አም ሀምባሪቾን በምክትል አሰልጣኝነት በመያዝ ክለቡን ወደ ከፍተኛ ሊግ ማሳደግ ችሏል።

✍ በ 2010 አም ቀጥታ ወደ ባህርዳር በማቅናት የማንጎ ምክትል በመሆን ባህርዳር ከተማ ወደ ፕሪሚየር ሊግ ማሳደግ ችሏል።

✍ በ 2011 አም ሀላባ ከተማን በምክትል አሰልጣኝነት የሰራ ሲሆን በሀላማ አመቱን ከጨረሰ ቡሀላ በቀጥታ ወደ የመጀመሪያው ክለብ ወደ ሆነው ጎፋ ባሬንቼን በ 2012 አም ተቀላቅሏል። በኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ ለሚሳተፈው ክለብ ክለብ በምድቡ ውብ የሆነ ማራኪ እንቅስቃሴ የሚጫወት ቡድን የሰራ ሲሆን ቡድኑ በምድቡ የተሻለ ውጤት በማምጣት በ 2013 አም በአዳማ ከተማ በተከናወነው የአንደኛ ሊግ ማጠቃለያ ውድድር አልፎ በውድድሩ ክስተት የሆነ ክለብ የሰራ ሲሆን በአጨዋወቱ ረገድ ለተመልካች ቀልብ የሚስብ አጨዋወት በመጠቅም አዳማ ለተገኘው የእግር ኳስ ተከታይ ያስደመመ ጫዋታ በማሳየት ወደ ከፍተኛ ሊግ ለማለፍ ጫፍ ደርሶ ስምንት ውስጥ ገብቶ ውድድሩን ማገባደድ ችሏል።

✅ አሰልጣኝ መኮነን ገላነህ #ዊሀ ተወልዶ ያደገው በ ውቢቷ የፍቅር ከተማ አርባምንጭ ሲሆን በወቅቱ በነበረው የኢትዮጵያ ሻምፒዮና ለተለያዩ ክለቦች በተጫዋችነት ማገልገል ችሏል። ይህ ሰው ወደ አሰልጣኝነት በክለብ ደረጃ የተቀላቀለው በ2008 አም ሲሆን ክለቡም በጥንካሬው የሚታወቀው በአንደኛ ሊጉ ድምቀት ከነበሩ አንዱ የደቡቡ ክለብ ለጎፋ ባሬንቼ እግር ኳስ ክለብ በዋና አሰልጣኝነት ለአንድ አመት ማገልገል ችሏል።

❓2014/15 አም የውድድር አመት መኮነን ገላነህ #ዊሀ የት እንመልከተው ይሆን?
✅ ታላቁ አሰልጣኝ ወደ ታችኛው ሊግ ወርዶ ተፈትኖ አልፏል።
👍 ስለዚህ ጥበበኛ አሰልጣኝ ከብዙ በጥቂቱ እንዲህ አልናቹህ። 🎙 #ዳጉ_ስፖርት የኢትዮጵያ ታችኛው ሊግ ብቸኛዋ ድምፅ

AFCON 2021 የአፍሪካ ዋንጫየሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ዳሰሳ

AFCON 2021 የአፍሪካ ዋንጫ
የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ዳሰሳ

የግማሽ ፍፃሜ ጫዋታ

ጥር 1 ተጀምሮ
ወደ መገባደጃው የደረሰው የአፍካ ዋንጫ 20 ሀገራትን አሰናብቶ 4 ሀገራትና 4 ጨዋታዎች ብቻ ቀርተውታል፡፡ እንዚህም ለፍፃሜ የሚደረጉ
ሁለት ጨዋታዎች፣ ለደረጃ የሚደረግ አንድ ጨዋታ እና ለዋንጫ የሚደረግ አንድ ጨዋታ ናቸው፡፡ ለዚህ ክብር የበቁ ሀገራትም ቀድሞ
በኢትዮጵያ ምድብ የሚገኙት ሁለቱ ሀገራት አዘጋጇ ካሜሮንና ቡርኪና ፋሶ፣ እንዲሁም የሊቨርፑሎቹ ክዋክብት የያዙት ግብፅና ሴኔጋል
ናቸው፡፡ እንዚህ ሀገራት የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎቻቸው ምን ይመስል እንደነበር እንመልከት

ካሜሮን በቶኮ
ኢካመቢ የ50ኛ እና 57ኛ ደቂቃዎች ጎል አስገራሚዋን ጋምቢያ ጉዞዋን የገታችበትን የ2 ለ 0 ድል አሳክታ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ተቀላቅላለች፡፡
ቶኮ ኢካመቢ በመድረኩ ያስቆጠራቸውን የጎሎች ብዛት ወደ አምስት አሸጋግሮ 6 ጎሎች ካሉት የቡድን አጋሩ ቪንሰንት አቡበከር ጋር
ለኮከብ ጎል አግቢነት ይፎካከራል፡፡ 

ቡርኪናፋሶ የሰሜን
አፍሪካዋን የአረብ ሀገር ቱኒዚያን በ45+3ኛ ደቂቃ ላይ በኦውታራ አማካኝነት ባስቆጠረችው በቸኛ ጎል 1 ለ 0 አሸንፋ ግማሽ ፍፃሜውን
የተቀላቀለች ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ጎል አስቆጣሪው አውታራ በ82ኛ ደቂቃ ላይ ከሜዳ በቀይ ካርድ ቢወገድም ቱኒዚያዎች ወደ ጨዋታው
ተመልሰው ጎል ማቆጠር ሳይችሉ ጨዋታው ተጠናቋል፡፡ 

አስገራሚ ፉክክር
ይታይበታል ተብሎ የተጠበቀው የግብፅና የሞሮኮ ጨዋታ እንደተጠበቀው ሆኖ ከ120 ደቂቃዎች ፍልሚያ በኋላ በግብፅ የ2ለ1 አሸናፊት
ተጠናቋል፡፡ ሞሮኮዎች በፍፁም ቅጣት ምት ጨዋታው ከተጀመረ ገና በ6ኛ ደቂቃ ላይ በሲፊያን ቦውፋል አማካኝነት ጎል አስቆጥረው የቸዋታውን
የአሸናፊነት ግምት ወስደው የነበር ቢሆንም በስነልቦና ጠንካራ የነበሩት ግብፆች ከእረፍት መልስ በ53ኛ ደቂቃ በኮከባቸው ሞሀመድ
ሳላህ አማካኝነት ባስቆጠሩት ጎል አቻ ሆነው ጨዋታው ተጨማሪ 30 የመፎካከረያ ደቂቃዎች እንዲኖሩት አደረጉ፡፡ከእረፍት መልስ ተከላካዩን
ሂጋዚይን ቀይሮ ገብቶ የነበረው አማከዩ ትሬዜጌትልክ በ100ኛ ደቂቃ ላይ በአስደናቂ ብስለት ከሳላህ የተሻገረለትን ኳስ በጥሩ አጨራረስ
አስቆጥሮ ግብፆችን አሸናፊ አድርጓል፡፡ በጫወታው ከስፖርታዊ ጨዋነት ውጭ መጎሻሸሞች የነበሩት ቢሆንም ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ
የግብፅ ተጫዋቾች የሞሮኮን ተጫዋቾች ያፅናኑበት መንገድ አነጋጋሪ ሆኖ ነበር፡፡

ሴኔጋል ምህረት
የለሽ መሆኗን አሳይታ ግማሽ ፍፃሜውን በተቀላቀለችበት የመጨረሻ ጨዋታ ኢኳቶሪያል ጊኒን 3ለ1 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡ ሴኒጋሎች
በ28ኛ ደቂቃ ላይ ከሳዲዮ ማኒ የተሸገረለትን ኳስ አጥቂው ዳይዲዩ አስቆጠሮ መሪ መሆን ቢችሉም ኢኳቶሪያል ጊኒዎች ከእረፍት መልስ
በቡይላ አማካኝነት በ57ኛ ደቂቃ ላይ ጎል አስቆጥረው አቻ ሆነው ወድ ጨዋታው ለመመለስ ሞክረው ነበር፡፡ ምህረት የለሾቹ ኩያቴና
ሳር በ68ኛ እና 79ኛ ደቂቃዎ ላይ ባስቆጠሩት ተከታታይ 2 ጎሎች ሴኔጋሎች 3ለ1 በሆነ ውጤት አሸንፈው ግማሽ ፍፃማን ተቀላቅለዋ፡፡

በግማሽ ፍፃሜ
ጨዋታዎች ቡርኪናፋሶ እና ሴኔጋል እንዲሁም ግብፅ እና አዘጋጇ ካሜሩን 
የሚፋለሙ ይሆናል፡፡
የግማሽ ፍፃሜ ጫዋታ
የግማሽ ፍፃሜ
ጨዋታዎች 

Ø  ቡርኪና ፋሶ ከ   ሴኔጋል

ሮብ ምሽት 4፡00
ሰዓት

Ø  ካሜሩን  ከ ግብፅ                   

ሀሙስ ምሽት 4፡00 ሰዓት


©️ ዳጉ Sport by Wosen ፔጥሮስ

በአርባምንጭ ከተማ ለሚካሄደው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን 13ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ወደ ከተማዋ ለተጓዙ ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል ተደረገ።

በአርባምንጭ ከተማ ለሚካሄደው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን 13ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ወደ ከተማዋ ለተጓዙ ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል ተደረገ።

የአርባ ምንጭ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ምክትል ከንቲባ አቶ ደረጄ ጳውሎስ፣ የከተማው አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተመስገን ሰይድ፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ም/ዋና ፀሐፊ እና የጠቅላላ ጉባኤ አዘጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ገ/ስላሴ ጥሪ የተደረገላቸው የከተማና የዞን አመራሮች በዛሬው እለት ወደ ከተማዋ ለገቡት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ኘሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ፣ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት፣ ዋና ፀሐፊ አቶ ባሕሩ ጥላሁን ፣ የጉባኤው አባላት፣ ዳሬክተሮችና ጥሪ ለተደረገላቸው እንግዶች በአርባምንጭ ከተማ አየር ማረፊያ  አቀባበል ተደርጓላቸዋል።

ለጉባኤው ዝግጅት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባኤ አዘጋጅ ኮሚቴ አባላት ወደ  አርባምንጭ ከተማ ከሁለት ቀናት በፊት በመገኘት የቅድመ ዝግጅት ሥራውን ከአርባምንጭ ከተማ የዝግጅቱ አስተባባሪዎች ጋር በጋራ እየሰራ የሚገኝ ሲሆን ታህሳስ 23 – 24 / 2014 ዓ.ም ሲምፖዚየም እና ጠቅላላ ጉባኤው ይካሄዳል።
Via #EFF
JOIN T.me/Dagu_Sport

Design a site like this with WordPress.com
Get started